
አርሶ አደርን ለማቋቋም ቅንጅታዊ ሥራዎች ወሳኝ ናቸው፡፡
አርሶ አደርን ለማቋቋም ቅንጅታዊ ሥራዎች ወሳኝ ናቸው፡፡
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም
አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ከመሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ ጋር በመሆን የአርሶ አደሩን መሬት ልኬት የመውሰድ፣ ፋይል የማደራጀት ስራ እተሰራ የቆየ መሆኑን የአርሶ አደር ልማት ቡድን መሪ ወ/ሮ ደግነሽ በደዊ ገልጸዋል፡፡እስከ አሁን ስካን የተደረገ ፋይል(ነባርና አዲስ) አርሶ አደር 15813 ፣በአርሶ አደር ልጅ 3299፣ አጠቃላይ ድምር19112 ነው ተብሏል፡፡በተጨማሪም እስከ አሁን ስካን የተደረገ የይዞታ ዓይነት(ነባርና አዲስ)ለመኖሪያ 12569፣ለእርሻ 6646፣ለግጦሽ 5899፣ለድርጅት 1564፣ልዩ በህር ያለው 206፣ አጠቃላይ ድምር 26884 ሲሆን እስካሁን ልኬት የተወሰደላቸው(ነባርና አዲስ)አርሶ አደር 16640፣በአርሶ አደር ልጅ 2261፣አጠቃላይ ድምር 18901 ነው ተብሏል፡፡
በተጨማሪ ለመኖሪያ12618፣ለእርሻ 7144፣ለግጦሽ 6554 ለድርጅት 1615 ልዩ በህር ያለው 204፣አጠቃላይ ድምር 28135 እንደሆነ ተነግሯል፡፡ እስከ አሁን ድጅታል መታወቂያ ያገኙ አርሶ አደር 15973፣በአርሶ አደር ልጅ 2213 ድምር 18186 እንደሆነ እናአርሶ አደሮቹን መልሶ ለማቋቋምና ለማልማት ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ቅንጅታዊ ሥራዎች እንደሚቀጥሉ ቡድን መሪዋ ገልጸዋል፡፡
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments