ይህን ያውቁ ኖሯል?
ይህን ያውቁ ኖሯል?
አዲስ አበባ፣ቀን 7/2/2018 ዓ.ም
የእብድ ውሻ በሽታ የየቫይረስ በሽታ ሆኖ ከፍተኛ የአንጎል መጉረብረብን በሰዎች እና በሌሎች ደመ-ሞቃት እንስሳት ላይ የሚያስከትል ነው። ቅድሚያ ምልክቶቹ ትኩሳት እና በተነከሱበት ቦታ ማሳከክ/ማቃጠልን ያካትታል። እነዚህ ምልክቶች ከሚከተሉት አንድ ወይም የበለጡ ምልክቶች አስከትለው ይመጣሉ:- ሃይል የታከለባቸው የሰውነት እንቅስቃሴዎች ከቁጥጥር ወጭ የሆ መሸበር፣ የውሀ ፍራቻ, የሰውነት ክፍልን ለማንቀሳቀስ አለመቻል፣ ግራ መጋባት፣ እና ህሊናን መሳት። ምልክቶቹ ከታዩ በኋላ፣ የእብድ ውሻ በሽታ በአብላጫው ሁልጊዜ ሞትን ያስከትላል። በበሽታው በመያዘዎ እና ምልክቶቹ መታየት የሚጀምሩበት የጊዜ ገደብ በአብዛኛውን ጊዜ ከአንድ እሰከ ሶስት ወራት ባሉት ጊዜ ውስጥ ነው። ሆኖም ግን፣ ይህ የጊዜ ገደብ ከሳምንት ባነሰ እና ከአመት በበለጠ ጊዜ ሊለያይ ይችላል። የጊዜ ገደቡ የሚወስነው የበሽታ አምጭው ረቂቅ ህዋስ ወደ የማዕከላዊ የነርብ ስርዓት ለመድረስ በሚፈጅበት እርቀት ነው።
የእብድ ውሻ በሽታ ወደ ሰዎች የሚተላለፈው በሌሎች እንስሳት ነው። በበሽታው የተበከለ እንስሳ ሌላ እንስሳ ወይም ሰው ሲቧጭር ወይም ሲናከስ የእብድ ወሻ በሽታ ሊተላለፍ ይችላል። የተበከለ እንስሳ ምራቅ ከሌላ እንስሳ ወይም ሰው የሰውነት ፈሳሽ አመንጭ ህዋስ ያሉበት ማስተላለፊያ ጋር ከተነካካ የእብድ ወሻ በሽታ ሊተላለፍ ይችላል።አብዛኛዎቹ በሰዎች ላይ የተከሰት የእብድ ወሻ በሽታዎች መንስሄዎች የውሻ ንክሻ ናቸው። በአብዛኛው ውሾች የእብድ ውሻ በሽታ ባለባቸው ሀገራት ከ99% በላይ የእብድ ውሻ በሽታ ክስተቶች መንስኤዎች የውሻ ንክሻዎች ናቸው። በአሜሪካዎች ውስጥ፣ የሌሊት ወፎች በአብላጫ የተለመደ የእብድ ውሻ በሽታ መንስኤ ናቸው፣ እናም ሰዎች ላይ ከ5% በታች የእብድ ውሻ በሽታ ክስተቶች መንስኤ ውሾች ናቸው። ረጃጅም የፊት ጥርስ ያላቸው ትንንሽ አጥቢ እንስሳት/አይጥ/ሽኮኮ/.. በእበድ ወሻ በሽታ የመያዝ እድላቸው በጣም ኢሚንት ነው። የእብድ ወሻ በሽታ ረቂቅ ህዋስ ወደ አንጎል የሚጓዘው ፐርፈሪያል ነርብስ በመከተል ነው። በሽታው ሊታወቅ የሚችለው ምልክቶቹ ከጀመሩ በኋላ ነው።
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments