የሙያዊ ሥነ-ምግባር ክፍተት የፍትህ መጓደልን ያስከትላል፡፡
የሙያዊ ሥነ-ምግባር ክፍተት የፍትህ መጓደልን ያስከትላል፡፡
አዲስ አበባ፤ ህዳር 11 ቀን 2018 ዓ.ም
በዓለም አቀፍ ለ22ኛ ጊዜ በሐገራችን ለ21ኛ ጊዜ ትውልድን በሥነ-ምግባር፤ተቋምን በአሰራር ! በሚል መሪ ቃል የሚከበረው የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ የፓናል ውይይት ተካሄደ፡፡
በአዲስ አበባና ከተማ አስተዳደር አርሶ አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረው የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ በሙያዊ ሥነ-ምግባር ዙሪያ ዳይሬክተሮች፣ቡድን መሪዎችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር የፓናል ውይይት ያካሄደ ሲሆን የሙያዊ ሥነ-ምግባር ክፍተት መኖሩ የሚያደርሰው ጉዳትና መፍትሄዎቹ በሚል ርዕሰ ጉዳይ ውይይት ተደርጓል፡፡
ሥነ-ምግባር ማለት የአንድ ሰው ጥሩ ወይም መትፎ ጎን ውጤቱ የሚለካበት እንደሆነና ከሞራልና አመለካከት አንጻር የሚገመገምበት እንደሆነ በውይይቱ ተነስቷል፡፡ስለሆነም የሥነ-ምግባር መጓደል አካባቢን፣ማህበረሰብን፣ኢኮኖሚን እና ማህበራዊ ኑሮን እንደሚጎዳ ተወያዮቹ አንስተዋል፡፡
በማህበረሰቡ ዘንድ በተደጋጋሚ ግንዛቤን መፍጠር፣ጠንካራ የህግ ማእቀፍ መዘርጋት እና ተጠያቂነትን ማስፈን የሥነ-ምግባር መጓደልን ማስተካከል እንደሚቻል ተብራርቷል፡፡
በመጨረሻም ከተሳታፊዎቹ ለተነሱት ሀሳብና አስተያየቶች ምላሽ ተሰጥቶባቸው ውይይቱ ተጠናቋል፡፡
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments